በምስራቅ ጎጃም ዞን የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢዎች በሚሊሻዎች ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የሰማያዊ ፓርቲ ምክትል የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ በቃሉ አዳነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ታዛቢዎቹ ‹‹ከአሸባሪ ፓርቲ ጋር አብራችሁ እየሰራችሁ ነው›› እየተባሉ ድብደባ እየተፈፀመባቸው እንደሆነ የገለጹት አቶ በቃሉ ቀሪዎቹን ‹‹ከአሸባሪ ፓርቲ ጋር ሲሰሩ አገኘናቸው ብለን እንከሳችኋለን›› እያሉ እያስፈራሯቸው ነው ብለዋል፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር የምትገናኙበት ነው በሚልም ስልካቸውን […]
