ሜሪስቶፕስ ኢንተርናሽናል በኢትዮጵያ ክሊኒኮችን ከፍቶ የሥነ ተዋልዶና የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን መስጠት ከጀመረ 21 ዓመታት ሆኖታል፡፡ ተቋሙ በኢትዮጵያ 31 ክሊኒኮች ሲኖሩት ከእነዚህም ውስጥ ስድስቱ አዲስ አበባ ይገኛሉ፡፡ ተቋሙ ከ570 ክሊኒኮች ጋርም በመጣመር የሥነ ተዋልዶና የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ ሜሪስቶፕስ የማዋለድ አገልግሎት የሚሰጥ አንድ ክሊኒክ ሲኖረው በወር 210 እናቶችን ያዋልዳል፡፡ ተቋሙ ሁለት ተጨማሪ ሆስፒታሎችን በባሕር ዳርና በአዳማ […]
