ኬንያ ውስጥ ሰሞኑን በስደተኞችና ፍልሰተኛ ነዋሪዎች ላይ እየካሄደ ያለው ፍተሻ፣ የቤት ለቤት አሰሳና የጅምላ እሥራት የፈጠረው የውጥረት ድባብ የሰብዓዊ መብቶች ጥያቄዎችን እያስነሣ ነው፡፡ቪኦኤ ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተለና ዘገባዎችንም እያወጣ ነው፡፡ከኢትዮጵያዊያኑ ስደተኞች መካከል እያነጋገርን ነው፡፡የኬንያ ፖሊስ ያለህጋዊ ፈቃድ ሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የውጭ ሀገር ስደተኞችን ዒላማ ባደረገው ዘመቻችው ከአንድ ሺህ የሚበልጡ ሰዎችን መርምረናል፥ ሁለት መቶ ሃያ አምስት ሰዎችን […]
