ኢሳት ዜና :-ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ የህወሃት አጀንዳ ነው በማለት ተቃውሞ ሲያሰሙ የነበሩትን የኦህዴድ አባላት ለማሰር እንቅስቃሴ መጀመሩን ከኦህዴድ ምንጮች የደረሱን ዜና አመለከተ።ለደህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዳይገለጥ የፈለጉት እነዚህ አባላት እንደተናገሩት፣ ድርጅቱ አዲሱን የአዲስ አበባ ፕላን በተመለከተ አባላቱ እንዲወያዩበት ቢያስደርግም፣ በውይይቱ ወቅት የተቃውሞ ሃሳባቸውን ሲያሰሙ የነበሩትን ሰዎች ማሰር ተጀምሯል። በርኴታ የድርጅቱአባሎች ደግሞ ከእስራት ለመሸሽ […]
