የእሥራኤል ጦር የጋዛ ሠላማዊ ሕዝብን መግደል፤ ማቁሠል፤ ማሰቃየቱን የሚቃወመዉ ሕዝብ ባለፈዉ ሳምንት ከቺካጎ-እስከ ለንደን፤ ከፓሪስ እስከ ኢስታንቡል፤ ከበርሊን እስከ ቴሕራን የሚገኙ አደባባዮችን በሠልፍ አጥልቅልቋቸዉ ሰነበተ።የእሥራኤል ደጋፊዎችም ተሠልፈዋል።ግን ቁጥሩ ከተቃዋሚዎቹን አንፃር ኢምንት የሚባል አይነት ነበር።ምዕራባዊ ዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ፤ ሊባኖስ፤ ዱባይ ሌላዉ ቀርቶ የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊዎች ሮኬት በሚወርድባት ቴል አቪቭም የእሥራኤልን መንግሥት በመቃወም-አደባባይ የወጡ ነበሩ። እስራኤል በፍልስጤሞች […]
