በዛሬው ዕለት አብርሃ ደስታ ጊዮርጊስ በሚገኘው የአራዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ አብርሃ ወደፍርድ ቤቱ ሁለት እጆቹ በካቴና እንደታሰሩና በአራት መሳሪያ በታጠቁ ፖሊሶች ታጅቦ ሲገባ በስፍራ የነበሩ ሰዎች ሞቅ ያለ ጭብጨባ አቅርበውለት ነበር፡፡ በፊቱ ላይ መረጋጋት እና ፈገግታ የሚነበብበት አብርሃ፣ በቻለው አቅም ሰዎችን ሰላምታ ለመስጠት ጥሯል፡፡ አብርሃ ወደችሎት ከገባ በኋላ፣ የታጠቁ ፖሊሶች […]
