ከጳጉሜ5 2006 ጀምሮ በጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የመዥንገር ዞን ጎደሬ ወረዳ በተፈጠረ ግጭት ለጊዜው ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ለህልፈተ ህይወትና ስደት መዳረጋቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ። በአካባቢው ለረጅም አመታት በመምህርነት እንዳገለገሉ የሚናገሩት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ግለሰብ ራሳቸውን የአካባቢው ነባር ብለው በሚጠሩት ነዋሪዎችና መጤ በሚሏቸው ደገኞች መካከል መፈጠሩን ገልፀዋል። አቶ ተስፋዬ ጌታነህ በአካባቢው የብሄረ አማራ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ […]
