የዓለም ዓቀፍ “እስልምና እምነት” ወኪል ነኝ በሚል ስያሜ ለራሱ የሠየመው “IS” የተባለውን ነውጠኛ አክራሪ የእስልምና ቡድንን የተቀላቀለ በዜግነት እንግሊዚያዊ የሆነ፣ ከኢትዮጵያ ወላጆች የሚወለድ የአስራ ሰባት አመት ወጣት በኢራቅ መገደሉን የቅርብ ዘመዶቹ ለሰንደቅ ገልፀዋል። የሞቹ ወጣት አጎት የሆኑት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ለዝግጅት ክፍላችን ስለአሟሟቱ ሲገልጽ፤ “መሐመድ 17 ዓመት ወጣት ልጅ ነው። በጣም የምወደው ልጅ ነበር። […]
