ብስራት አማረ ከቤተመንግስት ዘርፎ የወሰደው የጃንሆይ ወርቅ ከአገር ያወጣው አቶ መለስ ዜናዊ በተሳፈሩበት አውሮፕላን እንደነበረ አንድ ከፍተኛ የደህንነት ምንጭ አጋለጠ። በአሜሪካ ኦሀይ ግዛት የሚኖረው የቀድሞ የሕወሐት አባልና የደህንነት ሹም ብስራት አማረ ከቤተመንግስት ከዘረፈው የጃንሆይ ወርቅ ጋር በተያያዘ እንዲታሰር መደረጉን ያስታወሰው ምንጩ ይህን ውሳኔ ያስተላለፉት ጥቂት የፓርቲው አመራሮች መሆናቸውን ጠቁሟል። ብስራት በሆለታ እስር ቤት እንዲታሰር ቢደረግም […]
