በስዊዘርላንድ ባንክ ክሬዲት ስዊዝ የሚመራው የአውሮፓ አበዳሪ ባንኮች ጥምረት፣ ኢትዮጵያ ላቀደችው የአዋሽ – ወልዲያ የባቡር ፕሮጀክት ለማቅረብ የተስማማውን 1.4 ቢሊዮን ዶላር ብድር አዘገየ፡፡ ባንኩ የተጠቀሰውን ብድር ያዘገየው የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ያቀረበው የአካባቢና ማኅበራዊ ተፅዕኖ ጥናት ክሬዲት ስዊዝ ከሚከተለው ‹‹ኢኳቶሪያል ፕሪንሲፕል›› ከተሰኘ የአካባቢና ማኅበራዊ ተፅዕኖ መመዘኛ ደረጃ ጋር፣ ሙሉ በሙሉ መጣጣም ባለመቻሉ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል፡፡ […]
