የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ቃሊቲ ጉምሩክ ጽሕፈት ቤት ከፍተኛ ኦፊሰር፣ አቶ ዘመን ይሰማው 40,000 ብር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል በሚል ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡ የፌዴራል ሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን በተጠርጣሪው ላይ የመሠረተው ክስ እንደሚያስረዳው፣ የፈረንሣይ ኤምባሲ ሠራተኛ በነበሩት በሚስተር ሚሼል ሪቻርድ ስም የገባ ተሽከርካሪን፣ አቶ ተዋበ ዘለቀ የተባሉ ግለሰብ በ450,000 ብር ይገዛሉ፡፡ ግለሰቡ ተሽከርካሪውን […]
