- በመንግሥትና በፓርቲው መካከል ጥብቅ ትስስር ለመፍጠር ታቅዷል - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንባሩ ዋና ጸሐፊና የመንግሥት ምክር ቤት መሪ ይሆናሉ ገዢው ፓርቲ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) አዲስና ልዩ የተባለ የአደረጃጀት ለውጥ ለማድረግ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተሰማ፡፡ የአዲሱ አደረጃጀት ዓላማ ጥብቅ የሆነ ትስስርን በመንግሥትና በፓርቲው መካከል መፍጠር እንደሆነ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ […]
