በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ከሚገኙት ሰባት የዞን 9 ጦማርያን እና ሶስት ወዳጅ ጋዜጠኞች ስድስቱ ጦማርን እና ሶስቱ ጋዜጠኞች ዛሬ ግንቦት 18/2007 ዓ.ም የፌደራሉ ከፍተኛው ፍ/ቤት ቀርበዋል፡፡ መዝገቡ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው ሁለት ጉዳዮችን ለማየት ሲሆን፣ አንደኛው አቃቤ ህግ በኤግዚቢትነት አሉኝ ያላቸውን ኤግዚቢቶችና 12 ሲ.ዲዎች መዝገብ ቁጥራቸውን በመጥቀስ […]
