የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የመንግሥት ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫ ነው፡፡ በቢሊዮን የሚገመት ሀብት ለኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ ይውላል፡፡ ‹‹ከዚያም ከዚህም›› ተለምኖ በብድር ተፈልጎ ለኬብል ዝርጋታ፣ ለገጠር ኤሌክትሪፊኬሽንና መሰል ሥራዎች ርብርብ ይደረጋል፡፡ ያም ሆኖ ኮርፖሬሽኑ የሕዝብ እርካታና አመኔታን ያገኘ እንዳልሆነ አስተያየት ሰጪዎች ያስረዳሉ፡፡በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል በዓል ሲሆን፣ የውጭ እንግዶች ከተማውን ሲጎበኙ፣ በትልልቅ አገራዊና […]
