ለ17 ዓመታት ያህል ፊፋን በፕሬዝዳንትነት የመሩት ስዊዘርላንዳዊው ሴፕ ብላተር አሁን ስልጣናቸውን እንደሚለቁ አስታውቀዋል። በሳቸውና በተቀሩት ጓደኞቻቸው ላይ አሜሪካ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል በማለት ከቀናት በፊት ምርመራ መጀመሯን ተከትሎ ፊፋ እየታመሰ ነው። ደቡብ አፍሪካም የዓለም ዋንጫን በሃገሯ ለማካሄድ ለፊፋ 10ሚሊዮን ዶላር ጉቦ መስጠቷን አምናለች። አሜሪካ የወንጀል ምርመራ መክፈቷን ተከትሎ የፊፋ ዋና መስሪያቤት የሚገኝበት ስዊዘርላንድ ወንጀል መርማሪዎችም በተናጥል […]
