ከመቶ ለሚበልጡ የኦሮሞ ተወላጆች ሞት ምክንያት የሆነዉ፣ አያሌ የኦሮሞ ተወላጆች ታስረዉ ለስቃይ አያያዝ የተጋለጡበት፣ እዉቅ የፖለቲካ መሪዎች፣ጋዜጠኞች፣ የሲቪክ ተቋማት አገልጋዮች ታፍነዉ የተወሰዱበት፣ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን የፈሰሰበት ደም ሳይደርቅ መመሪያዉ ወደ መሬት እየወረደ ነው ሲሉ የሱልልታ ነዋሪዎች ለቢቢኤን ገለጹ። የሱሉልታ ማዘጋጃ ቤት የገበሬዉን መሬት ለመንጠቅ ማስትወቂያ አዉጥቷል የሚሉት ነዋሪዎች፤ የማዘጋጃቤት ሰራተኞች በድምጽ ማጉያ መሬት መዉሰድ […]
