ድምፃዊ ኢዮብ መኰንን ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ባደረበት ድንገተኛ ሕመም ራሱን ስቶ በሕክምና ላይ እንደሚገኝ ታወቀ፡፡ በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የተገለጸው ኢዮብ የሕመሙ መንስዔ ስትሮክ መሆኑ ታውቋል፡፡ የቅርብ ጓደኞቹ ድምፃዊው ይህ ነው የሚባል ሕመም እንዳልነበረበትና ታሞ እንደማያውቅ ገልጸው፣ ባለፈው እሑድ ድንገት እጁ ላይ በተሰማው ስሜት ምክንያት ሐያት ሆስፒታል ለመታየት ቢሄድም ሙሉ ጤነኛ እንደነበር ተነግሮታል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ […]
