ኢንተርኔትን በመጠቀም የጽሁፍና የድምጽ መልእክቶች የምናስተላልፍባቸው አፕሊኬሽኖችን ጨምሮ ፌስ ቡክና ትዊተር በኢትዮጵያ የኦሮሚያና በአንዳንድ የደቡብ ክልሎች ካለፈው አንድ ወር ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ብሎምበርግ የአካባቢዎቹን ነዋሪዎች በመጥስ ዘግቧል፡፡ የስማርት ስልክ ተጠቃሚዎች በስልካቸው የጫኗቸውን አፕሊኬሽኖች በመጠቀም አገልግሎቶቹን ማግኘት አለመቻላቸውን በመጥቀስ የቴሌ ኮም አገልግሎት ለአገሪቱ በመስጠት ላይ የሚገኘውን መንግስታዊ ተቋም ይከሳሉ፡፡በወሊሶ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆነው ስዩም ተሾመ በስልክ […]
