የተለያዩ አገራትን አቋርጠው በስደት ወደ አሜሪካ የገቡትና ፍሎሪዳ ታስረው የሚገኙ 11 ኢትዮጵያውያንን በግዳጅ ወደ አገር ቤት ለመመለስ ዝግጅት እየተደረገ እንደሆነ ተገለጸ። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት ሰፍኗል፣ ግለሰቦቹም ወደ ኢትዮጵያ ቢመለሱ ምንም አይሆኑም በሚል የአሜሪካ መንግስትን ያታለለው የኢትዮጵያ መንግስት፣ የታሳሪዎችን ዶክመንትም በራሱ ሰዎች እጅ እንዳስገባ ታውቋል። በዚሁ በፍሎሪዳ ክፍለ ግዛት ታስረው የሚገኙ 2 ኢትዮጵያውያን በቅርቡ ወደከፋ […]
