የቀድሞ የጋምቤላ ፕሬዚደንት አቶ ኦኬሎ አኳይ የጋምቤላ ጭፍጨፋን በተመለከተ ለፍርድ ቤት ማብራሪያ ሰጡ። የጭፍጨፋውን ሂደት በማዛባት፣ የተሳሳተ መረጃ ለህዝብ እንዲያቀርቡ በመገደዳቸውና ጭፍጨፋው የህሊና ሰላም ሰለነሳቸው ፕሬዚደንትነታቸውን ጥለው ድንበር አቋርጠው መሸሻቸውን በጽሁፍ ለፍርድ ቤቱ አስታውቀዋል። ከሰኔ ወር 1978 ጀምሮ በነርስነት የመንግስት ስራ መጀመራቸው፣ በኋላም እስከ ክልል ፕሬዚደንትነት በዘለቀው አገልግሎት 18 ዓመታት መቆየታቸውን ያስረዱትና የ8 ልጆች አባት […]
