የአውስትራሊያ መንግስት የዛሬ 15 ቀን በጋምቤላ ክልል ከ208 ሰዎች በላይ መገደላቸውንና 108 ህጻናትና ሴቶች መጠለፋቸውን ተከትሎ፣ዜጎቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይጓዙ ማሳሰቢያ አወጣ። የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳይና ንግድ ሚኒስትር በመግለጫው እንዳመለከተው፣ ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ለማድረግ እቅድ ያላቸው አውስትራሊያውያን ለጉዞ ከመዘጋጀታቸው በፊት የጉዞውን አስፈላጊነት መመርመር እንደሚገባቸው ገልጿል። የአልሻባብ አሸባሪዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ የመንግስት ህንጻዎች፣ ታሪካዊ ቦታዎችና የውጭ ዜጎች በሚያዘወትሩባቸው […]
