ዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይሲሲ) ከአፍሪካ ጋር አንድ ዓይነት ቋንቋ ማውራት ተስኖታል፡፡ 50ኛ ዓመቱን በቅርቡ ያከበረው የአፍሪካ ኅብረት የወቅቱ ሊቀመንበር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የመሪዎች ጉባዔ መጠናቀቅን አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አይሲሲን በዘረኝነት የከሰሱ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥና ከወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት የሚያመልጡን ለመያዝ የተቋቋመ ቢሆንም፣ አፍሪካውያኑን ማደን ብቸኛ ሥራው መሆኑን ኅብረቱ እንደሚቃወም […]
