እኔ የምለው…በመብራት፣ በውሃና በስልክ አገልግሎቶች አዲስ የተቆረቆርን አገር መሰልን አይደል? (ደቡብ ሱዳን እኮ ተሻለች!) ሰሞኑን በኢቴቪ የሰማሁት የውሃ ችግር ግን “የባሰ አለና አገርህን አትልቀቅ” የሚያሰኝ ነው፡፡ “ሰሜናዊቷ ኮከብ” እየተባለች በምትሞካሸው መቀሌ ከተማ 3 ወር ሙሉ ውሃ አልነበረም ተባለ፡፡ (አሁንስ የታለ?) የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢቴቪ ቅሬታቸውን ሲናገሩ፤ በውሃ እጦት ክፉኛ መሰቃየታቸውን ገልፀዋል፡፡ (ግን እንደኛ ሳይማረሩ!) እኔማ… የመቀሌ […]
