መቀመጫውን በኒውዮርክ ያደረገው ሲፒጄ የተሠኘው የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ጋዜጠኞችን በማሠርና በማንገላታት ኢትዮጵያ ከአለም ሁለተኛ ናት ማለቱን መንግስት እና በሃገሪቱ የሚገኙ የጋዜጠኞች ማህበራት አምርረው ሲያወግዙ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች በበኩላቸው፤ በእርግጥም ሃገሪቱ ጋዜጠኞችን እያሠረች ነው፤ ደረጃው ይገባታል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞች ህብረት ፕሬዚዳንት አቶ አንተነህ አብርሃም፤ “ሲፒጄ የሃገራችንን ስም ለማጥፋት ስለሚፈልግ ነው እንጂ፣ በፃፈው ፅሁፍ የታሠረ […]
