የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ስዊዘርላንድ ላይ ያሳረፈው የረዳት ፓይለት ሃይለመድህን ጉዳይ አነጋጋሪነቱ እንደቀጠለ ነው። የአውሮፕላን ጠለፋው ጉዳይም ከኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጋር የተያያዘ ፖለቲካዊ አንድምታ እንዳለው እየተነገረ ይገኛል። ይህን ተከትሎ ረዳት ፓይለቱ የሰራው ሥራ የሚደነቅ ነው በሚል በርካቶች ውዳሴን እያቀረቡለት ሲሆን “ረዳት ፓይለቱ በእጁ እንዳለው የተለያየ ሃገር ቪዛ በማንኛውም ጊዚ ከሃገር መውጣት ይችል ነበር፤ ሆኖም ግን […]
