የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት አንድነት ፓርቲ ለላከለት ማስጠንቀቂ ምላሽ መስጠቱን የአንድነት ዋና ጸሀፊ አቶ ስዩም መንገሻ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡ አቶ ስዩም መንገሻ ለፍኖተ ነፃነት እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት በቅርቡ አንድነትን በ“አሸባሪነት” የሚፈርጅ ዘጋቢ ፊልም ማቅረቡን ተከትሎ አንድነት ፓርቲ ድርጅቱ ምላሽ እንዲሰጥ ጥር 1 ቀን 2006 ዓ.ም ደብዳቤ ጽፏል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለደብዳቤው ምላሽ ባለመስጠቱም አንድነት በድጋሚ […]
