ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሚያዝያ ፩ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. የወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር የሕዝብ ግንኙነት ሓላፊ የሰጡትን መግለጫ አንብቤ ነበር፡፡ ከመግለጫቸው ውስጥ እጅግ የገረመኝና ይህን ጽሑፍ እንድጽፍ ያደረገኝም አክራሪነትን በተመለከተ የሰጡት ትርጓሜ ነው፡፡ መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳንን በአክራሪነት እንዳልፈረጀ ከገለጡ በኋላ፣ ‹‹ይህ ሲባል ግን እንደ ማንኛውም ተቋም የተቀደሰውን ዓላማ የሚያራክሱ፣ ማኅበሩን ወዳልኾነ አቅጣጫ የሚወስዱ ግለሰቦች አይኖሩም […]
