የስድስቱን ጦማርያንና የሁለቱን (የኤዶምና የተስፋለምን)ጉዳይ በመከታተል በፍርድ ቤት እየወከሏቸው የሚገኙት የህግ ባለሞያ አቶ አምሐ ሁልግዜም የህግ ደምበኞቻቸው ፍርድ ቤት ከቀረቡ በኋላ ግቢው ውስጥ ውጪ ለምንጠብቃቸው ጋዜጠኞች በዝጉ ችሎት ምን እንደተከናወነ ያለምንም መሰላቸት ያስረዳሉ፡፡በትናንትናው የፍርድ ቤት ውሎም ጠበቃው ከዋናው ግቢ ውጪ አሰፍስፈን ለጠበቅናቸው ጋዜጠኞች መረጃ አድርሰውናል፡፡ለተባባሪነታቸው፣ድካም ሳይነበብባቸው፣አንተ ወይም አንቺ ከየትኛው ሚዲያ ነህ/ሽ ሳይሉ ለሚዥጎደጉድላቸው ጥያቄ ምለሽ […]
