ከኢትዮጵያ ቴሌኮም ይልቅ ህልሜን አመንኩት! ባለፈው ሳምንት በህልሜ ያየሁት ነገር አስገራሚ ነው፡፡ በአብዛኛው በህልማችን የምናየው ነገር የግል ህይወታችን ላይ የሚያተኩር ይመስለኛል፡፡ መቼም ናላውን ከሚያዞረው የኑሮ ውድነት ሃሳብ ወጥቶ ስለአገሩ ባለ ሁለት ዲጂት የኢኮኖሚ ዕድገት በህልሙ የሚያይ ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡ (ቢያይማ ከኑሮ ውድነት ይወጣ ነበር!) ስለ አገሪቱ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መጎልበት ወይም ስለ ስልጡን የፖለቲካ ባህል መዳበር […]
