ከእንግዲህ ወዲያ ግዜው ለዶክተር ህወሓት የዋዛ አይመስልም፡፡ ታግዬለታለሁ፤ ልማትም ዴሞክራሲም አጎናፅፌዋለሁ፣ ታማኝ ደጀኔም እሱ ነው ብላ የምትመካበት የትግራይን ህዝብ በአይነቱ የተለየና ከባድ ፍጥጫ እየገጠማት ነው፤ ህወሓት በመስቀለኛ መንገድ ላይ ቆማለች፡፡ በሙስና የተጨማለቀውን መዋቅርዋ ሳይውል ሳያድር ካላፀዳች፤ በመልካም አስተዳደር እጦት በከፍተኛ ደረጃ የተማረረውን ህዝብ በኣስቸኩዋይ ካላረመች፤ የውሸት ዳታን እየጋገርኩ ህዝብን በባዶ ተስፋ እደልለዋለሁ ማለትዋን አቁማ ቀጥተኛ […]
