የቀድሞ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራር አባል የነበሩትና አሁን የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር መሪ አቶ ሌንጮለታ፤ ትግላቸውን በሃገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ለማከናወን ወደ አዲስ አበባ በቅርብ ጊዜ እንደሚጓዙ አስታወቁ። ከዓመት በፊት ዋሽንግተን ዲሲ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ለውይይት ዝግጁ መሆናቸውን በደብዳቤ ያሳወቁት የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር አመራር አባላት፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ውይይት አድርገው ወደ ሀገር የመመለስ እቅድ ነበራቸው። […]
