ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ በተካሄዱት አራት ጠቅላላ ምርጫዎች የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በተወዳደሩበት በአደዋ የምርጫ ክልል ለመጀመሪያ ጊዜ በዘንድሮ ምርጫ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ኢሕአዴግን ወክለው እንደሚወዳደሩበት ለማወቅ ተችሏል፡፡ በመጪው ግንቦት በሚካሄደው አምስተኛ ጠቅላላ ምርጫ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር የትውልድ ቦታና ጠንካራ የፖለቲካ ይዞታ ወክለው፣ ለተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩት የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር […]
