ባሳለፍነው ሐሙስ በሰሜን ኬንያ በሚገኘው ጋሪሳ ዩኒቨርስቲ ሰቅጣጭ ዜና የሰማንበትን ድርጊት የመራው የቀድሞው የናይሮቢ ዩኒቨርስቲ የህግ ተማሪ የነበረው የ24 ዓመቱ ሞሀመድ አብድራሂም አብዱላሂ መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ የሙሀመድ ወላጅ አባት አብዱላሂ ዳቃሪ የመንግስት ከፍተኛ ስልጣን የያዙና በጃምሁሪ አካባቢ የሚገኘውን ማንዴራ የተሰኘ ክልል የሚያስተዳድሩ መሆናቸውም ነገሩን አወዛጋቢ አድርጎታል፡፡ በናይሮቢ ዩኒቨርስቲ የህግ ዲፓርትመንት ቆይታው በጓደኞቹ አባብሞ እየተባለ ይጠራ […]
