ትላንት አመሻሽ ላይ በዲሲ 16ኛው መንገድ “የእኛ እድር” የተሰኘ ድራማ ይታይ ነበር። ዝግጅቱን ለመታደም ከኢየሩስና አብራት ከምትማረው ታዳጊ ኤልሳ ጋር በስፍራው ተገኘን። ድራማው ይጀመራል ከተባለበት ጊዜ ለ1 ሰዓት ተኩል ዘግይቶ ነበር። (ሃበሻና ቀጠሮ መቼ እንደሚታረቁ አይታወቅም)…ዝግጅቱ እስኪጀምር ወግ ቀጠልን። ታዳጊ ኤልሳ አሜሪካ ከአባቷ ጋር የመጣችው ከ5 አመት በፊት ነበር። የ16 አመቷ ኤልሳ በገፅታዋ ብሶትና መከፋት […]
