በጎንደር ወገራ ወረዳ ንዑስ ወረዳ ገደብዬ የቀበሌ አስተዳዳሪዎችና የማዘጋጃ ቤት ሹሞች አስረኛ ክፍል ጨርሰው ስራ ፈትተው የተቀመጡትን ወጣቶች እንዲሁም ዘጠነኛ ክፍልን በመማር ላይ የሚገኙ ታዳጊ ወጣቶችን ጭምር “በ5000 ብር ደመወዝ ስራ እንቀጥራችኋለን” በሚል ማማለያ አሽበልብለው በስልጠና ስም ባንድ አዳራሽ ውስጥ አጉረው በፖሊስ በማገት በመጨረሻም ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ጭነዋቸዋል፡፡ ለውትድርና በግዳጅ የታፈሱት በርካታ ቁጥር ያላቸው […]
