ቱኒዝያ ለአራት ቀናት በዘለቀው ሀገር አቀፍ ብጥብጥ ተጠያቂ ናቸው ያለቻቸውን ሁለት መቶ ስልሳ ሰዎች ማሠሯን አስታወቀች። እስረኞቹ በአመጽ ድርጊት እና ነውጥ በመቀስቀስ እንደሚከሰሱ ሼምስ ኤፍ ኤም የተሰኘ የሀገሪቱ ሬዲዮ ዘግቧል። በቱኒዝያ ያለው የኢኮኖሚ ሁኔታ እና የሥራ አጥነት መባባስ በመላ ሀገሪቱ ለተቀሰቀሰው ተቃውሞ ሰበብ እንደሆነ ተነግሯል። የቱኒዝያ መንግሥት ትናንት ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ንጋቱ 11 ሰዓት […]
