መቀመጫውን በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ከተማ ያደረገው የኖርዌይ ኤምባሲ ዜጎቹ ወደ ኦሮሚያ ክልል በሚያደርጉት ጉዞ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄን እንዲያደርጉ ማክሰኞ አሳሰበ። በክልሉ በምዕራብ አርሲ ዞን አካባቢ የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎች ማሳሰቢያን ያሰራጨው ኤምባሲው የጸጥታ ስጋት በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮሚያ ከተሞች መሆኑንም አመልክቷል። በክልሉ ያሉም ሆነ ወደ ክልሉ ለመጓዝ እቅድ ያላቸው የኖርዌይ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄን በማደረግ በጉዞአቸው […]
