የታንዛኒያ ኢሚግሬሽን ጉዳይ በኪሊማንጃሮ ግዛት በቁጥጥር ስር የሚገኙ 74 የኢትዮጵያ ፍልሰተኞች ወደ ሃገራቸዉ የሚመለሱበትን መንገድ እንዲያመቻች የዓለም አቀፉ ፍልሰት ድርጅት (IOM )ጥሪ አቅርቧል። ፍልሰተኞቹ በታንዛኒያ ዉስጥ በህገ-ወጥ ዝዉዉር ታስረዉ የእስር ጊዜያቸዉን የጨረሱ ሲሆኑ፤ የታንዛኒያ መንግስት ከ3 ሳምንታት በፊት በኬንያ ድምበር በኩል ወደ ሃገራቸዉ እንዲመለሱ ለማድረግ ቢሞክርም የኬንያ የድመበር ጠባቂዎች ኢትዮጵያዉያኑን ወደ ኬንያ ድምበር እንዳይገቡ ከልክሏቸዋል። […]
