ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁን ለሦስት ቀናት በኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ወደሀገር ውስጥ የመጡት የእስራኤል የደህንነት ሠራተኞች የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናትን በፈሳሽ ኬሚካል እጃቸውን እንዲታጠቡ አስገደዱ። ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ዕለት በሸራተን አዲስ ጠቅላይ ሚኒስተር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ በተገኙበት በተካሄደው የቢዝነስ ፎረም ላይ ተካፋይ ለመሆን በተደረገላቸው ጥሪ የተገኙ የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ከእሥራኤል የደህንነት ሠራተኞች […]
