በቃለቲ ወህኒ ቤት በጥይት ተመተው ከቆሰሉት 2 ታሳሪዎች መካከል አንዱ ተደብድቦ መገደሉ ታወቀ፡፡ ከ2 ቀናት በፊት ቅዳሜ ነሐሴ 28/2008 ለሊት የቃሊቲ እስርቤት ጠባቂዎች 2 እስረኞችን ገድለው 2ቱን ደግሞ ማቁሰላቸው ተዘግቦ ነበር፡፡ ዛሬ በደረሰኝ መረጃ መሠረት ከ2ቱ በጥይት ቆስለው ከተረፉት እስረኞች መካከል አንዱን የእስርቤቱ ታጣቂዎች እሁድ ነሐሴ 30/2008 በአሰቃቂ ሁኔታ ደብድበው እንደገደሉት ለማወቅ ችያለሁ፡፡ ይህም በቃሊቲ […]
