ከኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባርና ከአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የወቅቱን የኢትዮጵያ ሁኔታ በማስመልከት የተሰጠ መግለጫና ለሁሉም ነፃነት ፈላጊ ወገኖች የቀረበ ጥሪ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ለነፃነት፣ ለፍትህ፣ ለእኩልነትና ለትክክለኛ ዲሞክራሲ የሚያደርጉት የብዙ ሺህ ንፁሃን ዜጎችን የሕይወት መስዋዕትነት የጠየቀ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ከመቀጠልም አልፎ ወደከፍተኛ ደረጃ ተሸጋግሯል፡፡ የዛሬዉ የሕዝባችን ትግል የአገዛዙን የከፋፍሎ መግዛት ግንብ ንዶ በተባበረ መንፈስና በአንድ […]
