የአሜሪካ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት አጣጥለውታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት አፈ ቀላጤ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ መግለጫውን ‹‹የኢትዮጵያን መረጋጋት እና ሰላም ከማይመኙ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ጥቂት ሰራተኞች የተሰጠ መግለጫ ነው፡፡›› ሲሉ ተችተውታል፡፡ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ ላይ፣ አስቸኳይ አዋጁ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ ተገቢውን ስራ እንዳያከናውን ማነቆ […]
