በገበሬዎች የተማረከውን የጦር መሣሪያ ለማስመለስ በሃይማኖት አባቶች ሙከራ አድርጎ ያልተሳካለት የወያኔ ጦር ምሽግ እየቆፈረ እንደሆነ የጎበዝ አለቆች አስታወቁ። የጎበዝ አለቆቹ እንደሚሉት ዛሬ ሰላም ይወዳርዳል በማለት 15 የማረክናቸውን ወታደሮች ለቀንላቸው ነበር። ሆኖም ወያኔዎች የማረካችሁትን መሣሪያም መልሱልን አሉን። ወታደሮቹን መልቀቅ አልነበረብንም፤ የሃይማኖት አባቶች ሲያስቸግሩን ሰላም ይውረድ ብለን ነበር የሸኘናቸው። ግን ዘግይተን መሳሳታችን አወቅን። ሊገሉን ስለመጡ መሞት ነበረባቸው። […]
