በዳባት ወረዳ በጃኖራ ቀበሌ ካለፉት 2 ሳምንታት ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ጦርነት ዛሬ ቀጥሎ የዋለ ሲሆን፣ ታጋዮች የያዙትን ምሽግ ሰብሮ መግባት ያልቻለው የአገዛዙ ጦር፣ ከባድ መሳሪያዎችን በመተኮስ የስነ ልቦና ጫና ለመፍጠር እየሞከረ ነው። ከጦር ግንባሩ የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በአካባቢው በብዛት የሰፈሩት ወታደሮች ሞርታርና ዲሽቃ እየተኮሱ አካባቢውን ሲደበድቡ ውለዋል። የግንባሩን ቃል አቀባይ በቀጥታ ለማግኘት ባንችልም፣ ከአካባቢው ምንጮች […]
