የህወሓት ደጋፊዎች የአቶ አርከበ ሚና መቀነስ በአቶ አባይ ምክንያት እንደሆነ ያስባሉ። እንደኔ ግን አርከበ የተገለለው በአባይ ወልዱ ሳይሆን በመለስ ነው። መለስ ስልጣን በጣም ከመውደዱ የተነሳ ለስልጣኑ የሚፈካከሩና አደጋ የሚደቅኑ ዓቅም ያላቸው የህወሓት ሰዎች ሲያርቅና ሲያጠፋ ነበር። መለስ ዓቅም ያለው ሰው አይወድም፤ ለስልጣኑ ስለሚያሰጉ። ለዚህም ነው አቶ አርከበ ተስፋ ቆርጦ ከፖለቲካ እንዲርቅ የተለያየ ተፅዕኖ ሲያረግበት የነበረው። […]
