ምንም ዛሬ ህወሃቶች በቅጥፈት ፕሮፓጋንዳ ሊያረሳሱት ቡሞክሩም እነሱ በ1998 ከሻብያ ጋር በዝርፊያ ክፍፍል ከመጣላታቸው እና በሰበብ ባስባቡ ጦርነት ከመዳደረሳቸው በፊት የሚያውቃቸው የኢትዩጵያ ህዝብ መቼም የማይዘነጋው እውነታ አለ። መለስ ዜናዊ የኢትዩጵያን ”ባንዲራ ጨርቅ ነው“ ብሎ ካንቋሸሸባት ግዜ ጀምሮ በየቢሮዋቸው፣ ሰርጋቸው እና በግል ቤታቸው ብቻ ሳይሆን በየአመታዊ በዓሉም ሆነ ሌላ የማህበራዊ በአል ላይ ህወሃቶች የእራሳቸውን ባንዲራ እንጂ […]
