ገና የ22 ዓመት ኮረዳ ናት ሳዑዲ ዓረቢያዊቷ ሁዳ አል፡፡ የመናዊው አራፋት መሐመድ ጣሂር ደግሞ የ25 ዓመት ጉብል፡፡ እሱ በሳዑዲ ዓረቢያ ስደተኛ ሆኖ በአንድ የሞባይል ስልክ መሸጫ ተቀጥሮ ይሠራ ነበር፡፡ ፍቅር የተባለው ረቂቅ ነገርም ሁለቱን ወጣቶች አቀራረባቸው፣ አስተሳሰባቸው፣ አፋቀራቸው፡፡ ውሎ ሲያድርም ከአንድ ጣራ ሥር ለመኖር አስወሰናቸው፡፡ ይሁንና የሁዳ ወላጆች ጋብቻቸውን አልፈቀዱም ነበር፡፡ ‹‹በቡሃ ላይ ቆርቆር›› እንዲሉም […]
