በትላንትናው ዕለት አንድ የኢቦላ በሽተኛ የላይቤሪያ ዋና ከተማ ሞኖሮቪያ ውስጥ ካለው የኢቦላ መታከሚያ ኤልዋ ሆስፒታል አምልጦ ወደ ከተማዋ ገበያ ቦታ አምርቶ ነበር፡፡ በሽተኛው ከሆስፒታል አምልጦ ወደ ገበያ የሄደበት ምክንያት አሳዛኝ ነው – ረሀብ፡፡ በሆስፒታሉ ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ በመጥፋቱ ረሀብ ያስገደደው በሽተኛ የሚበላ ፍለጋ በሽተኝነቱን የሚገልጽ ምልክት እጁ ላይ እንደታሰረ ወደ ገበያ ቦታ ያመራል፡፡ ቢቢሲ ባሰራጨው […]
