የባህርዳር ከተማ የባጃጅ ሾፌሮች የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለፁ፡፡ በከተማው ባጃጆች ከአንድ መስመር ውጭ እንዳይሰሩ ከመከልከላቸው ባሻገር ኮንትራት ጭናችኋል በሚልና በሌሎችም ሰበቦች በየቀኑከፍተኛ ቅጣት ስለሚጣልባቸውና ቅጣቱ ከሚያገኙት ገቢ በላይ በመሆኑ የስራ ማቆም አድማ ለማድረግ መገደዳቸው ተናግረዋል፡፡ ታክሲዎች በማይደርሱበት አካባቢ ጭምር ኮንትራት ሲጭኑ 400 ብር ቅጣት እንደሚጣልባቸው የገለፁት ሾፌሮቹ፣ በሌሎች አጋጣሚዎችም በየቀኑ […]
