ፓርላማው (የኢህአዴግ ጉባኤ) በሙሉ ድምጽ በዛሬው ዕለት የፍትህ ሚንስትር የነበሩትን አቶ ጌታቸው አምባዬን ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ‹‹ዋና አቃቤ ህግ ››በማድረግ በዕጩነት ማቅረባቸውን አጽድቋል፡፡ይህው ፓርላማ ጌታቸው ይመሩት የነበረውን ፍትህ ሚንስትርን ማፍረሱን ማስታወቁም አይዘነጋም፡፡ የፌደራል አቃቤ ህግ በተቋም ደረጃ ራሱን ችሉ እንዲቋቋም አዋጅ ሲወጣለትም ዋና አቃቤ ህጉ ከፖለቲካ ሹመት ውጪ እንዲሆን ብዙዎች ቢወተውቱም ጌታቸው ቁጢጥ ብለውበታል፡፡ […]
